|
አዲሱ የአፍሪካ ህብረት የስብሰባ ማዕከል ተመረቀ
|
|
አዲስ አበባ፣ ጥር 19 ፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ) 200 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር በሚጠጋ ወጭ የተገነባው አዲሱ የአፍሪካ ህብረት የስብሰባ ማዕከል ተመረቀ። በቻይና መንግስት ሙሉ ወጭ የተገነባው ማዕከል ምረቃ ላይ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ተገኝተዋል።
|
|
|
|
|
|
|
|
|
|
|
|
|
|
|
|
የኢጋድ ልዩ የመሪዎች አስቸኳይ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቀቀ
|
|
አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ) 20ኛው የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) ልዩ የመሪዎች አስቸኳይ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቀቀ። በኢጋድ አባል ሀገራት መካከል የመሰረተ ልማት ዝርጋታን በማጠናከርና ነጻ የገበያ ቀጠናን በማቋቋም የአካባቢውን ሀገራት ኢኮኖሚያዊ ውህደት ከፍ ወዳለ ደረጃ ላይ ለማድረስ የሚያስችል ውሳኔ መተላለፉን የኢጋድ ሊቀ መንበርና የኢፊዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ተናግረዋል።
|
|
|
|
|
|
20ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት ስብሰባ እየተካሄደ ነው
|
|
አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ) 20ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት ስብሰባ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። የህብረቱ አባል አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እየተሳተፉበት የሚገኘው የምክር ቤቱ መደበኛ ጉባኤ እሁድ ለሚጀመረው የመሪዎች ጉባኤ አጀንዳዎችን እየቀረፀ ይገኛል።
|
|
|
|
|
|
|
|
|
|
|