Fana: At a Speed of Life!

ህወሃት አስቸኳይ ድርጅታዊ ጉባኤውን ሊያካሂድ ነው

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 24፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ህወሃት አስቸኳይ ድርጅታዊ ጉባኤውን ታህሳስ 25 እና 26 ቀን በመቐለ ከተማ ሊያካሂድ ነው፡፡

ድርጅቱ በሚያካሄደው ጉባኤ የኢህአዴግን ውህደት በሚመለከት ተወያይቶ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የህወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ በትናትናው ዕለት በሰጠው መግለጫ÷ አስቸኳይ ጉባኤውን የሚያስተባብር  አዘጋጅ ኮሚቴ በማቋቋም አስፈላጊውን ዝግጅት ሲያካሂድ መቆየቱን ነው የገለፀው፡፡

በጉባኤው ከህወሃት መሰረታዊ ድርጅቶች የተወከሉ አባላት ፣ ምሁራን ፣ የሀይማኖት መሪዎች ፣ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ ተብሏል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.