ህወሓት በዋድላ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ከ42 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ውድመት አድርሷል
የሽብር ቡድኑ በወረዳው በነበረው ቆይታ በሆስፒታሉ ላይ ከፍተኛ የንብረት ዘረፋና ውድመት መፈጸሙንም ነው ሥራ አስኪጁ ያብራሩት፡፡
ሆስፒታሉ ከ200 ሺህ በላይ ለሆኑ ሰዎች አገልግሎት የመስጠት አቅም የነበረው ሲሆን÷ አሁን ላይ በአሸባሪው ህወሓት 42 ሚሊየን 500 ሺህ ብር የሚገመት የንብረት ዘረፋና ውድመት ስለተፈጸመበት ምንም አይነት አገልግሎት መስጠት የማይችልበት ደረጃ ላይ ነው ብለዋል ሥራ አስኪያጁ፡፡
በዚህም ድንገተኛና ተከታታይ ህክምና የሚፈልጉ ዜጎች እየሞቱና በበሽታ እየተሰቃዩ ነው መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡
ሆስፒታሉ ወደ መደበኛ ስራው ተመልሶ በበሽታ የሚሰቃዩ ዜጎችን ለመታደግ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ድጋፍ እንዲያደርጉ አቶ ተስፋዬ ፋንታሁን ጥሪ ማቅረባቸውን ከመቄት ወረዳ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡