Fana: At a Speed of Life!

ማለዳውን ከዲሲ ወደ አዲስ አበባ እየበረረ ባለ አውሮፕላን ውስጥ ያሉ ተሳፋሪዎች የ10 ሺህ 400 ዶላር ድጋፍ አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ማለዳውን ከዲሲ ወደ አዲስ አበባ እየበረረ ባለ አውሮፕላን ውስጥ ያሉ ተሳፋሪዎችን በማስተባበር የ10ሺህ 400 ዶላር ድጋፍ በማሰባሰብ በአይዞን ኢትዮጵያ አካውንት ድጋፍ አድርገዋል፡፡

ድጋፉን ያስተባበሩት በበረራው የነበሩ የተወሰኑ ተጓዦች ሲሆኑ፥ በቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕልንማረፊያ በሚገኘው የአይዞን ኢትዮጵያ የንግድ ባንክ ሂሳብ ገቢ እድርገዋል።

በርካታ ኢትዮጵያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በተደረገላቸው ወደ ሃገር ቤት ግቡ ጥሪ ምላሽ እየሰጡ ናቸው።

ወደ ሃገር ቤት የሚገቡትም በተዘጋጀው የድጋፍ ማሰባሰቢያ ማእከላት በጦርነቱ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች መልሶ ማቋቋም እና ለወደሙ ተቋማት ድጋፍ እያደረጉ ይገኛሉ።

በቆንጅት ዘውዴ

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.