Fana: At a Speed of Life!

ሩስያ የኮሮና ቫይረስ ክትባት መስጠት ጀመረች

አዲስ አበባ፣ ህዳር 27፣ 2013 (ኤፍቢሲ) ሩስያ በወረርሽኙ ከፍተኛ ተጋላጭነት ውስጥ ለሚገኙ ዜጎቿ የኮሮና ቫይረስ ክትባት መስጠት ጀመረች፡፡

ክትባቱ እየተሰጠ የሚገኘው ለዚሁ ተብለው በተከፈቱ አዳዲስ ክሊኒኮች ነው ተብሏል፡፡

ይህ ስፑትኒክ ቪ የተሰኘው ክትባት በ70 ክሊኒኮች ነው በትናትናው ዕለት መሰጠት የተጀመረው፡፡

ይህንን ተከትሎም ሩስያ በሰፊው የኮሮና ቫይረስ ክትባትን በመስጠት የመጀመሪያዋ ሀገር ሆናለች፡፡

ክትባቱ በመጀመሪያ እየተሰጠ የሚገኘው ከፍተኛ ተጋላጭነት ላለባቸው ለህክምና ባለሙያዎች፣ ለመምህራን እና ለማህበራዊ አገልግሎት ሰጪዎች ነው ተብሏል፡፡

ክትባቱ በ21 ቀናት ልዩነት ለሁለት ያህል ጊዜ እንደሚሰጥ ነው መረጃ የሚያሳየው፡፡

ሆኖም ተመራማሪዎች በክትባቱ ስራ ላይ መዋል ስጋታቸውን የገለጹ ሲሆን የመጨረሻውን የቤተሙከራ ደረጃ እንዳላጠናቀቀም ተሰምቷል፡፡

እስካሁን በሩስያ ከ2 ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ ሰዎች በወረርሽኙ የተያዙ ሲሆን 42 ሺህ 684ቱ ደግሞ ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡

ምንጭ፡-ቢቢሲ

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤

ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ

ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.