Fana: At a Speed of Life!

ሰሜን ኮሪያ በኮቪድ19 ምክንያት በቶኪዮ ኦሊምፒክ እንደማትሳተፍ አስታወቀች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 28፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ሰሜን ኮሪያ በኮቪድ 19 ምክንያት በጃፓኑ ቶኪዮ ኦሊምፒክ እንደማትሳተፍ አስታወቀች፡፡

ፒዮንግያንግ ከከቪድ19 ጋር ተያይዞ የአትሌቶችን ጤንነት ለመጠበቅ በማሰብ በውድድሩ እንደማትሳተፍ አስታውቃለች፡፡

ሰሜን ኮሪያ ታሪካዊ የተባለውን ውይይት ካደረገች በኋላ በ2018 በተዘጋጀው የክረምት ኦሊምፒክ ላይ 22 አትሌቶቿን ወደ ደቡብ ኮሪያ መላኳ ይታወሳል፡፡

የአሁኑ የሰሜን ኮሪያ ውሳኔ ታዲያ ደቡብ ኮሪያ ከዘወትር ባላንጣዋ ጋር ለመወያየት የሰነቀችውን ተስፋ የሚያጨልም ነው ተብሏል፡፡

የኪም ጆንግ ኡን አስተዳደር የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በሀገሪቱ እንደሌለ በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቆይቷል፡፡

የጤና ባለሙያዎች በአንጻሩ በሀገሪቱ ኮሮናቫይረስ አልተከሰተም የሚለው ነገር የማይሆን ነው  ብለዋል፡፡

ምንጭ፦ አልጀዚራ እና ቢቢሲ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.