Fana: At a Speed of Life!

ሱዳን የኢትዮጵያን ድንበር በመውረር የአፍሪካ ቀንድን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ ጥላለች- የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 6 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የወቅቱ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታ ድርጅት (ኢጋድ) ሊቀመንበር ሱዳን የኢትዮጵያን ድንበር በመውረር የአፍሪካ ቀንድን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል ተግባር ላይ መሰማራቷ የሚያሳዝን ነው ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሱዳን ምንም እንኳን የኢጋድ ሊቀመንበር ብትሆንም የኢትዮጵያን መሬት ወራ፣ ሰላማዊ ዜጎችን አፈናቅላ አሁንም ተጨማሪ መሬቶችን ለመውረር የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመች ነው ብሏል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ሱዳን የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በትግራይ ክልል ህግን የማስከበር እርምጃ ሲሰማራ ከወረረችው የኢትዮጵያ መሬት ሰራዊቷን እንድታስወጣ እና ወደ ራሷ እንድትመለስ ጫና እንዲፈጥር በትዊትር ገጹ ላይ በማሰፈረው ፅኁፍ ጥሪ አቅርቧል።

ሚኒስቴሩ ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ 1972 የማስታወሻ ልውውጥ መሰረት የድንበር ልዩነቱን በግጭት መፍቻ መንገዶች መፍትሄ ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን አስታውቋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.