Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

በፕሪሚየር ሊጉ ፋሲል ከነማ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ18ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ፋሲል ከነማ ወደ አሸነፊነት የተመለሰበትን ውጤት አስመዝግቧል፡፡ ፋሲል ከነማን ከጅማ አባ ጅፋር ያገናኘው ጨዋታ በፋሲል ከነማ 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡ ጅማ አባ ጅፋር ሙሃመድ ኑር ናስር ባስቆጠራት ጎል እስከ እረፍት ሲመራ ቢቆይም ከእረፍት መልስ ይሁን እንዳሻው እና ኦኪኪ ኦፎላቢ ባስቆጠሯቸው ጎሎች ፋሲል 3 ነጥብ ማግኘት ችሏል፡፡ ማምሻውን በተካሄደ ጨዋታ ደግሞ ሲዳማ ቡና ሐዋሳ ከተማን አሸንፏል። ሲዳማ ጨዋታውን 3 ለ 1…
Read More...

በ18ኛ ሳምንት ፕሪሚየር ሊግ ሀዲያ ሆሳና ከአርባምንጭ ከተማ ጋር አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ሚያዝያ 3፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አስገራሚ ትዕይንት ያስተናገደው የሃዲያ ሆሳዕና እና አርባምንጭ ከተማ ጨዋታ 4 አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል፡፡ 8 ጎሎች በተቆጠሩበት የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ አርባ ምንጭ ከተማ እስከ 80 ደቂቃ ሃዲያ ሆሳናን 4 ለ 1 ሲመራ ቢቆይም ነብሮቹ በ10 ደቂቃዎች ውስጥ በተከታታይ ባስቆጠሯቸው ጎሎች ነጥብ ተጋርተው ወጥተዋል፡፡…

የኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግ ኩባንያ የተለያዩ የቅጣት ውሳኔዎችን አሳለፈ

አዲስ አበባ፣ሚያዝያ 3፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪሚየርሊግ ኩባንያ በ17ኛው ሳምንት ጨዋታዎች ላይ በታዩ የስነ ምግባር ግድፈቶች ላይ የቅጣት ውሳኔ አሳልፏል፡፡ አዳማ ከተማ ከጅማ አባ ጅፋር ጋር በነበረው የ17ኛ ሳምንት ጨዋታ የክለቡ ደጋፊዎች የእለቱን ዳኛና የተጋጣሚ ቡድን አሰልጣኝን አፀያፊ ስደብ መሳደባቸውን ተከትሎ 50 ሺህ ብር እንዲከፍል መወሰኑን…

ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቴኳንዶ ሻምፒዮና ውድድር አሸናፊ ሆነች

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በሁለተኛው የአፍሪካ ቴኳንዶ ሻምፒዮና ውድድር አሸናፊ ሆነች። ለሁለት ቀናት በራስ ኃይሉ ስፖርት ትምህርትና ስልጠና ማዕከል ሲካሄድ የነበረው ሻምፒዮና ተጠናቋል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቴኳንዶ ሻምፒዮና በሁለቱም ጾታዎች በ24 ወርቅ፣ በ23 ብርና በ33 ነሐስ በድምሩ 80 ሜዳሊያዎችን…

በ2022ቱ የሆላንድ ሮተርዳም ማራቶን አትሌት ፌቨን ሃይሉ አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በየዓመቱ በሆላንድ በሚከናወነው የሮተርዳም ማራቶን በሴቶች ምድብ ኢትዮጵዊቷ አትሌት ፌቨን ሃይሉ አሸንፋለች፡፡   ፌቨን ርቀቱን በ2 ሰዓት ከ22 ደቂቃ ከ01 ማይክሮ ሰከንድ በማጠናቀቅ ነው አሸናፊ የሆነችው፡፡   በወንዶች ምድብ በተከናወነው የማራቶን ውድድር ደግሞ ትውልደ ኢትዮጵያዊው…

ክላረንስ ሲዶርፍ ከታላቁ የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ጋር አዲስ አበባ ገብቷል

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 2፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) የቀድሞው የሪያል ማድሪድ እና ኤሲ ሚላን ኮኮብ ክላረንስ ሲደሮፍ የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ጋር አዲስ አበባ መጥቷል፡፡ በአፍሪካ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ጉዞ ከሚያደርግባቸው አራት አገራት መካከል አንዷ በሆነችው ኢትዮጵያ ባለ ትልቁ ጆሮ ዋንጫ ዛሬ በሸራተን አዲስ ሆቴል ለዕይታ በቅቷል ። ከዲሞክራቲክ ኮንጎ…

የአፍሪካ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን አቶ ታምራት ፈይሳን በድጋሜ ፕሬዚዳንት አድርጎ መረጠ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አቶ ታምራት ፈይሳ የአፍሪካ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን በፕሬዚዳንትነት እንዲመሩ ለሁለተኛ ጊዜ ተመርጠዋል። ጠቅላላ ጉባኤው ባካሄደው የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ምርጫ÷ አቶ ታምራት ፈይሳ የአፍሪካ ቴኳንዶ ፌዴሬሽንን ለቀጣይ አራት ዓመታት እንዲመሩ መርጧቸዋል። አቶ ታምራት ላለፉት አራት ዓመታት  ፌዴሬሽኑን…