ስፓርት
ኬፕ ቨርዴ ወደ ጥሎ ማለፉ ተቀላቀለች
አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ኬፕ ቨርዴ ወደ ጥሎ ማለፉ የተቀላቀለች የመጀመሪያዋ ሀገር ሆናለች፡፡
በዛሬው የአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታ ኬፕ ቨርዴ ሞዛምቢክን 3 ለ 0 አሸንፋለች፡፡
ጎሎቹንም÷ ቤቤ፣ ያን ሜንዴስ እና ኬቪን ሌኒ አስቆጥረዋል፡፡
በመጀመሪያው ዙር ጨዋታ ኬፕ ቨርዴ ጋናን 2 ለ 1 መርታቷ ይታወሳል፡፡
ኬፕ ቨርዴ በ6 ነጥብ ምድቡን በመምራት ከወዲሁ ጥሎ ማለፉን መቀላቀሏን ስታረጋግጥ÷ ግብጽ በ2 ነጥብ በምድቡ የደረጃ ሠንጠረዥ በሁለተኛ ደረጃ ለይ ትገኛለች፡፡
እንዲሁም…
Read More...
የአፍሪካ ዋንጫ አዘጋጇ አይቬሪኮስት በናይጄሪያ ተሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ዋንጫ አዘጋጇ አይቬሪኮስት በናይጄሪያ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ተሸነፈች፡፡
የናይጄሪያን የአሸናፊነት ጎል ዊሊያም ትሮስት ኤኮንግ በ55ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል፡፡
ቀደም ብሎ ከዚህ ምድብ በተደረገ ጨዋታ ጊኒ ቢሳው በኢኳቶሪያል ጊኒ 4 ለ 2 ተሸንፋለች፡፡
በምድብ ሁለት ምሽት 5 ሰዓት ላይ ግብጽ…
በፕሪሚየር ሊጉ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፋሲል ከነማን 1 ለ 0 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፋሲል ከነማን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የቅዱስ ጊዮርጊስን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ አማኑኤል ኤርቦ አስቆጥሯል፡፡
በተመሳሳይ ቀን 9 ሰዓት ላይ በተካሄደ ጨዋታ ሻሸመኔ ከተማ ሀምበሪቾ ዱራሜን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
በፕሪሚየር ሊጉ የ11ኛ ሳምንት መርሐ…
በአፍሪካ ዋንጫ ኢኳቶሪያል ጊኒ- ጊኒ ቢሳውን 4 ለ 2 አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ ዋንጫ ኢኳቶሪያል ጊኒ- ጊኒ ቢሳውን 4 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸነፈች፡፡
የአፍሪካ ዋንጫ የ2ኛ ዙር የምድብ ጨዋታ መርሐ ግብር ሲቀጥል ምሽት 2 ሰዓት ላይ ኮቲዲቯር ከናይጄሪያ እንዲሁም 5 ሰዓት ላይ ግብጽ ከጋና የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
ሞሮኮ ታንዛኒያን 3 ለ 0 አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር በምድብ ስድስት የሚገኙት ሞሮኮ እና ታንዛኒያ ጨዋታቸውን አድርገዋል፡፡
ሮማን ሳዩስ ባስቆጠራት ብቸኛ ጎል ለእረፍት የወጣችው ሞሮኮ÷ በሁለተኛው አጋማሽ ኡናሂ እና የሱፍ ኤል ነስሪ ባስቆጠሯቸው ተጨማሪ ጎሎች ጨዋታውን 3 ለ 0 ረትታለች፡፡
በ70ኛው ደቂቃ ኖቫቲስ ሚሮሺን በቀይ ካርድ ያጣችው…
መቻል እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ11ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መቻል እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡
9፡00 ሠዓት ላይ ድሬዳዋ ከተማን የገጠመው መቻል ከንዓን ማርክነህ እና በኃይሉ ግርማ ባስቆጠሯቸው ጎሎች 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡
እንዲሁም 12፡00 ሠዓት ላይ ኢትዮጵያ መድንን ያስተናገደው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከመመራት…
ናሚቢያ ቱኒዚያን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ 5 ጨዋታ ናሚቢያ ቱኒዚያን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈች፡፡
ናሚቢያን አሸናፊ ያደረገችውን ግብ ሆቶ በ88ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡
በዚሁ ምድብ የሚገኙት ማሊና ደቡብ አፍሪካ ምሽት 5 ሰዓት ላይ የሚጫወቱ ይሆናል፡፡
ቀደም ብሎ በተደረገ የምድብ 4 ጨዋታ ቡርኪናፋሶ…