Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ቡርኪናፋሶ በተጨማሪ ሰዓት ባስቆጠረችው ግብ ሞሪታኒያን አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በምድብ 4 የማጣሪያ ጨዋታ ቡርኪናፋሶ በተጨማሪ ሰዓት ባስቆጠረችው ግብ ሞሪታኒያን 1 ለ 0 አሸነፈች። ለቡርኪናፋሶ የማሸነፊያ ግብን በርትራንድ ትራኦሬ በ96ኛው ደቂቃ ላይ ማስቆጠር ችሏል፡፡ በአፍሪካ ዋንጫ በምድብ 5 ጨዋታዎች ምሽት 2 ሰዓት ላይ ቱኒዝያ ከናሚቢያ እንዲሁም ከምሽቱ 5 ሰዓት ላይ ማሊ ከደቡብ አፍሪካ ጋር ይጫወታሉ፡፡
Read More...

ጆዜ ሞሪንሆ ከሮማ አሰልጣኝነታቸው ተባረሩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጆዜ ሞሪንሆ ከሮማ አሰልጣኝነታቸው መባረራቸው ተሰምቷል፡፡ ለስንብታቸው የቡድኑ ውጤት ማጣት እና ከዳኞች ጋር የሚፈጥሩት አለመግባባት ምክንያት መሆናቸው ተገልጿል፡፡ ሮማ በሴሪአው ካደረጋቸው የመጨረሻዎቹ ስድስት ጨዋታዎች አንዱን ብቻ ማሸነፍ የቻለ ሲሆን በኮፓ ኢታሊያም በላዚዮ መሸነፉ…

በአፍሪካ ዋንጫ ካሜሮን እና ጊኒ  በአቻ ውጤት ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ካሜሮን እና ጊኒ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል። የካሜሮንን ብቸኛ ግብ ማሪ ማግሪን ሲያስቆጥር ÷ የጊኒን ደግሞ ሞሃመድ ባዮ አስቀጥሯል፡፡ የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታ መርሐ- ግብር ሲቀጥል ምሽት 5 ሰዓት አልጀሪያ ከአንጎላ ይጫወታሉ፡፡

በፕሪሚየር ሊጉ ሲዳማ ቡና ባሕር ዳር ከተማን 2 ለ 0 አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ11ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሲዳማ ቡና ባሕር ዳር ከተማን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ወሳኝ ሶስት ነጥብ አሳክቷል፡፡ ቀን 12 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ የሲዳማ ቡናን ግቦች ጊት ጋትኩት እና ፍቅረየሱስ ተክለብርሃን አስቆጥረዋል፡፡ በጨዋታው የባሕርዳር ከተማው ተከላካይ ያሬድ ባዬ በፈጸመው ጥፋት በቀይ…

በአፍሪካ ዋንጫ ሴኔጋል ጋምቢያን 3 ለ 0 አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታ ሴኔጋል ጋምቢያን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡ የሴኔጋልን የማሸነፊያ ግቦች ፔፔ ጉዮ እና ላሚን ካማራ አስቆጥረዋል፡፡ በጨዋታው የጋምቢያው ተከላካይ ኢብራሂማ አዳምስ በፈፀመው ያልተገባ ባህሪ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል፡፡ የአፍሪካ ዋንጫ መርሐ ግብር ምሽት…

በአፍሪካ ዋንጫ ኬፕ ቨርዴ ጋናን 2 ለ1 አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኬፕ ቨርዴ ጋናን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸነፈች። የኬፕ ቨርዴን የማሸነፊያ ግቦች ሞንቴሮ እና ሮድሪጌዝ ሲያስቆጥሩ፥የጋናን ብቸኛ ግብ ደግሞ ጂኩ አስቆጥሯል። በተመሳሳይ በምሽት 2 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ ግብፅ እና ሞዛምቢክ 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡ ምሽት 2 ሰዓት ላይ…

በአፍሪካ ዋንጫ ናይጄሪያ እና ኢኳቶሪያል ጊኒ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ ዋንጫ የሁለተኛ ቀን ውሎ የተገናኙት ናይጄሪያ እና ኢኳሪያል ጊኒ 1 አቻ በሆነ ውጤት ተለያይተዋል፡፡ ቪክቶር ኦሲሜን ለናይጄሪያ እንዲሁም ጆሴፍ ማሽን ለኢኳሪያል ጊኒ ጎሎች አስቆጥረዋል፡፡ የአፍሪካ ዋንጫ መርሐ- ግብሮች ምሽት መካሄዳቸውን ሲቀጥሉ 2፡00 ሰዓት ላይ ግብጽ ከሞዛምቢክ ይገናኛሉ፡፡ በተመሳሳይ…