ስፓርት
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መቻል ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥብ ጣለ
አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው 10ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መቻል ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ አቻ ተለያይቷል፡፡
9፡00 ላይ ሐዋሳ ከተማን የገጠመው መቻል 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡
የመቻልን ጎሎችም ምንይሉ ወንድሙ እና ከንዓን ማርክነህ ሲያስቆጥሩ÷ የሐዋሳ ከተማን ብቸኛ ጎል አሊ ሱለይማን አስቆጥሯል፡፡
ውጤቱን ተከትሎም መቻል ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በእኩል 23 ነጥብ ፕሪሚየር ሊጉን መምራት ሲችል÷ ሐዋሳ ከተማ በነበረበት 12ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡…
Read More...
ለአፍሪካ ዋንጫ የተለያዩ ሀገራት ብሄራዊ ቡድኖች አቢጃን እየገቡ ነው
አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአይቮሪኮስት አስተናጋጅነት ለሚደረገው የ2023ቱ የአፍሪካ ዋንጫ የተለያዩ ሀገራት ብሄራዊ ቡድኖች ወደ አቢጃን እየገቡ ይገኛሉ፡፡
ትናንት ምሽት የካሜሮኑ የአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮን የሴኔጋል ብሄራዊ ቡድን ኮትዲቯር የገባ ሲሆን÷ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ማኪ ሳል ከልዑካን ቡድኑ ጋር አቢጃን ገብተዋል፡፡
የካሜሮኑ የአፍሪካ…
የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቀቁ
አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 10ኛ ሳምንት የውድድር መርሐ ግብር የመጀመሪያ ቀን ውሎ ሁለት ጨዋታዎች ተካሂደዋል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ ሻሸመኔ ከተማ እና ኢትዮጵያ ቡና ያካሄዱት ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡
የሻሸመኔ ከተማን ግብ አብዱልቃድር ናስር ሲያስቆጥር÷ኢትዮጵያ ቡናን አቻ ያደረገችዋን ግብ ደግሞ…
ፍራንዝ ቤከንባወር ከዚህ አለም በሞት ተለየ
አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)የቀድሞው የምዕራብ ጀርመን እና የባየርሙኒክ ኮከብ ፍራንዝ ቤከንባወር በ78 አመቱ ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል።
ቤከንባወር በ1974 ጀርመን የዓለም ዋንጫን ስታነሳ ብሄራዊ ቡድኑን በአምበልነት መምራት የቻለ ሲሆን ÷በ1990 ደግሞ የጀርመን ብሄራዊ ቡድንን በአሰልጣኝነት እየመራ የዓለም ዋንጫን ማንሳት ችሏል፡፡
ባለ…
በዱባይ እና ዥያሜን ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል አደረጉ
አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2024 የዱባይ እና ዥያሜን ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ አሸንፈዋል፡፡
በዱባይ በወንዶች የተካሄደውን ውድድር አትሌት አዲሱ ጎበና ሲያሸንፍ÷ ለሚ ዱሜቻ 2ኛ፣ ደጀኔ መገርሳ 3ኛ እንዲሁም አብዲ ፉፋ 4ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቀዋል፡፡
በዚሁ የውድድር መርሐ-ግብር÷ አትሌት አንተን አየሁ ዳኛቸው 6ኛ፣…
በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ወላይታ ድቻ ድል ቀንቷቸዋል
አዲስ አበባ ፣ ታኅሣስ 27 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ9ኛ ሣምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ወላይታ ድቻ ድል ቀንቷቸዋል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ በተካሄደ ጨዋታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሀምበሪቾ ዱራሜን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሯል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የማሸነፊያ ግቦች ባሲሩ ኡመር እና በረከት ግዛው ናቸው…
በፕሪሚየር ሊጉ ፋሲል ከነማ እና ኢትዮጵያ ቡና ድል ቀንቷቸዋል
አዲስ አበባ ፣ ታኅሣስ 26 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ9ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ፋሲል ከነማ እና ኢትዮጵያ ቡና ድል ቀንቷቸዋል።
ከቀትር በኋላ በተካሄደ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ድሬዳዋ ከተማን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
የፋሲል ከነማን የማሸነፊያ ጎሎች ጌታነህ ከበደ እና ናትናኤል ገብረጊዮርጊስ አስቆጥረዋል፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተካሄደ ጨዋታ…