Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ መንግስት በጀመረው ህግን የማስከበር ዘመቻ ላይ እየተሳተፉ ለሚገኙ የፀጥታ አካላት የገቢ ማሰባሰቢያ የባንክ አካውንቶች ይፋ ሆኑ

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 2፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ መንግስት በህወሃት ውስጥ ባለው ቡድን ላይ በጀመረው ህግን የማስከበር ዘመቻ ላይ እየተሳተፉ ለሚገኙ የፀጥታ አካላት ገቢ ለማሰባሰብ የባንክ አካውንቶች ይፋ መሆናቸውን አስታወቁ።
ምክትል ከንቲባ በህወሃት ጁንታ ወንጀለኛ ቡድን አመራሮች ላይ የተጀመረው ህግን የማስከበር ዘመቻ ላይ ፊት ለፊት እየተጋፈጠ እና በድል እየተወጣ ለሚገኘው ጀግናው የመከላከያ ሰራዊት፣ የአጎራባች ክልሎች ልዩ ሃይል እና የሚልሻ አባላት የላቀ ድጋፍ እና ክብር ለመስጠት በጋራ እንቁም ብለዋል።
በመሆኑም የገንዘብ ድጋፍ ለማሰባሰብ የተዘጋጁ የባንክ አካውንቶች የሚከተሉት ናቸው÷
• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፡- አራዳ ጊዮርጊስ ቅርንጫፍ 1000354000834 ወይም 1818
• የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ፡- ኦዳ ቅርንጫፍ 1000048019619
• አዋሽ ባንክ፡- ፊንፊኔ ቅርንጫፍ 01301854206200

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.