በመዲናዋ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች አሸባሪውን ሕወሃት የሚያወግዝ ሰልፍ አካሄዱ
አዲስ አበባ፣ ህዳር 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች አሸባሪውን ህወሃት በማውገዝ ሰልፍ አካሂደዋል።
ሰልፈኞቹ÷ የትግራይ ህዝብ እና ህወሓት አንድ አይደሉም ፣የትግራይ ህዝብ ኩሩ ኢትዮጵያዊ ነው፣በትግራይ ክልል የሚኖረው ህዝባችንን መንግስታችን ነፃ እንዲያወጣ እንጠይቃለን የሚሉ እና ሌሎች መፈክሮችን አሰምተዋል፡፡