Fana: At a Speed of Life!

በሙስና የተማረረው ግብፃዊ ታህሪር አደባባይ ላይ እራሱን በእሳት አቃጠለ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 4፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አንድ ግብፃዊ ግለሰብ ካይሮ በሚገኘው ታህሪር አደባባይ ላይ እራሱን በእሳት ማቃጠሉ ተነገረ።
ግለሰቡ አሁን ላይ በካይሮ በሚገኝ ሆስፒታል የህምና ክትትል እየተደረገለት እንደሚገኝም ነው ሬውተርስ በዘገባው ያሰፈረው።
ክስተቱን በተመለከተ እስከአሁን ድረስ ከመንግስት ባለስልጣናት የተሰጠ አስተያየት የለም።
በማህበራዊ ሚዲያዎች የተዘዋወረው ተንቀሳቃሽ ምስል እንደሚያሳየው እራሱን በእሳት ያያዘው ግለሰብ በሀገሪቱ ባለው ሙስና መማረሩን ሲግልፅ ነበር ተብሏል።
ግለሰቡ እራሱን በእሳት ከማቃጠሉ በፊት ከፍ ያለ ድምፅ እያሰማ ያለቅስ እንደነበርም ዘገባው አስፍሯል።
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.