በምዕራብ ሐረርጌ 220 የተለያዩ ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያዎችና የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ
አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 9 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በምዕራብ ሐረርጌ ሐብሮ ወረዳ 220 የተለያዩ ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያዎችና የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ፡፡
ክላሽን ጨምሮ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች፣ ቦምብ እና ሽጉጦች እንዲሁም ከ897 ሺህ ብር በላይ ግምት ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዛቸውን ኦ ቢ ኤን ዘግቧል፡፡
የወረዳው ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሳጂን ተመስገን ከድር ኮንትሮባንድ ሕጋዊ ንግድ ላይ ተጽዕኖ በመፍጠር የሃገር እድገትን እንደሚጎዳ ተናግረዋል፡፡
የሐብሮ ወረዳ ወንጀል ምርመራ ስራ ሂደት ኃላፊ ኢንስፔክተር ኃይለማሪያም ጥበቡ በበኩላቸው፥ ህብረተሰቡ ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያ አዘዋዋሪዎችን በመጠቆም እንዲተባበር ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን