Fana: At a Speed of Life!

በራችን ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ክፍት ነው – ቻይና

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በሯ እንደማይዘጋ፣ ይልቁንም የበለጠ ክፍት እንደሚሆን አስታወቀች፡፡

የቻይና ፕሬዚዳንት ቺ  ጂንፒንግ÷ ቻይና ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በሯ ሁልጊዜም ክፍት እንደሆነ በ2ኛው የተባበሩት መንግስታት የዓለም አቀፉ ዘላቂ የትራንስፖርት ኮንፈረንስ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ ተናገሩ፡፡

ፕሬዚዳንቱ ÷በወረርሽኙ ምክንያት በክፍለ ዘመናችን አይተን የማናውቃቸው ጉልህ ለውጦች ቢከሰቱም የዓለም እድገት እንዲሁም እየዘመነ የመጣው ዓለም አቀፋዊ የትራንስፖርት ትብብር ይለመልማል ብለዋል፡፡

በቀጣይም በመሠረተ ልማት ትስስር ፣ ባልተገደበ የንግድና የኢንቨስትመንት ፍሰት እንዲሁም በሥልጣኔዎች መካከል በሚደረጉ ሁለንተናዊ ግንኙነቶች አዲስ ምዕራፍ እንጽፋለን ነው ያሉት – ቺ ጂንፒንግ፡፡

ቺ – አክለውም ትራንስፖርት የኢኮኖሚ ደም ስር ነው ብለው÷ በሥልጣኔዎች መካከል ትስስር እንዲቀጥልና ዓለም እንደ አንድ መንደር እንድትቀራረብ የሚያስችል ዘርፍ መሆኑንም አንስተዋል፡፡

ቺ – በንግግራቸው ÷ የትራንስፖርቱ ዘርፍ እያደገ መምጣቱን ታሪክ አጣቅሰው አንስተዋል፤ በዘመናዊው ዓለምም የትራንስፖርቱ ዘርፍ እድገት ለኢኮኖሚ ትስስር እና ለህዝቦች ግንኙነት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል፡፡ የዘገበው ሲጂቲ ኤን ነው፡፡

በዓለማየሁ ገረመው

 

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.