የሲዳማ ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ልዑካን በክልሉ የሚገኙ የኢንቨስትመንት ልማት እንቅስቃሴዎችን ጎበኘ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ልዑካን በክልሉ የሚገኙ የኢንቨስትመንት ልማት እንቅስቃሴዎችን እና መሰረተ ልማቶችን ጎብኝቷል፡፡
በጉብኝቱ በዘርፉ ካሉ የኢንቨስትመንት መሰረተ ልማቶች አንዱ የሆነውን የይርጋለም የተቀናጀ አግሮ ኢንደስትሪ ፓርክ የተመለከቱ ሲሆን÷በዚህም በፓርኩ ውስጥ እየሰሩ ያሉ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ጎብኝተዋል፡፡
ፓርኩ በአጭር ጊዜ ውስጥ በዘርፉ እያሳየ ያለው አፈጻጸም አበረታች መሆኑ በጉብኝቱ ወቅት መገለጹን ከኢንቨስትመንት ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡