Fana: At a Speed of Life!

በቡሬ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በቡሬ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡
አደጋው ከሌሊቱ 10 ሰዓት 48 ሰዎችን ጭኖ ለመንፈሳዊ ጉዞ ከደንበጫ ወደ ላሊበላ በመጓዝ ላይ የነበረ ኮድ 3 የሆነ ቅጥቅጥ አይሱዙ የህዝብ ማመላለሻ መኪና ቡሬ ከተማ በመገልበጡ የደረሰ ነው፡፡
በአደጋው ሳቢያ የአራት ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ ከ15 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ቆስለዋል።
ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በቡሬ አስራደ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን ከቡሬ ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.