Fana: At a Speed of Life!

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ባህርዳር ከተማ ድሬዳዋ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) በ28ኛ ሳምንት በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ባህርዳር ከተማ ድሬዳዋ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በሜዳው እና በደጋፊው ፊት ጨዋታውን ላደረገው ባህርዳር ከተማ መናፍ አወል ብቸኛዋ የማሸነፊያ ጎል ማስቆጠር ችሏል፡፡

የጣና ሞገዶቹ ዘሬ ማሸነፋቸውን ተከትሎ ነጥባቸውን 33 በማድረስ ከወራጅ ቀጠና ሸሽተዋል፡፡

 

በቀጣይ ባህር ዳር ከተማ ከሰበታ ከተማ እና ኢትዮጵያ ቡና ጨዋታውን የሚያደርግ ሲሆን፥ በአንጻሩ ድሬዳዋ ከተማ ከአዳማ ከተማ እና ከፋሲል ከነማ ጋር ቀሪ ጨዋታውን ያደርጋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.