Fana: At a Speed of Life!

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ድል ቀንቶታል

አዲስ አበባ፣ግንቦት 13፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ24ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ድል ቀንቶታል፡፡

ከሀዋሳ ከተማ ጋር የተጫወተው ኢትዮጵያ ቡና 3 ለ 1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል፡፡

የኢትዮጵያ ቡናን የድል ጎሎች አላዛር ሽመልስ እና አማኑኤል ዮሃንስ እንዲሁም ዳግም ተፈራ በራሱ መረብ ላይ ሲያስቆጥር ብሩክ በየነ የሀዋሳ ከተማን ብቸኛ ጎል አስቆጥሯል፡፡

ኢትዮጵያ ቡና ዛሬ ማሸነፉን ተከትሎ በእኩል 37 ነጥብ ከሲዳማ ቡና ጋር 3ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል፡፡

ረፋድ ላይ በተደረገ ሌላ መርሃ ግብር አዲስ አበባ ከተማ ከጅማ አባጅፋር አንድ አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.