Fana: At a Speed of Life!

በቶኪዮ ኦሎምፒክ ዛሬ የሚጠበቁ የፍፃሜ እና የማጣሪያ ውድድሮች

አዲስ አበባ ፣ሐምሌ 27፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)በቶኪዮ ኦሎምፒክ ዛሬ ከሰዓት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይጠበቃሉ፡፡

ዛሬ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በሚደረገው የ5000 ሜትር ወንዶች ማጣሪያ ውድድር እንዲሁም ከቀኑ 9፡25 ላይ በሚደረገው የ800 ሜትር ሴቶች ፍፃሜ ላይ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይወዳደራሉ፡፡

በ800 ሜትር ኢትዮጵያን ወክላ ሃብታም አለሙ ትሮጣለች፡፡

በ5000ሜትር ወንዶች ማጣሪያ ጌትነት ዋለ፣ ንብረት መላክ እና ሚልኬሳ መንገሻ እንደሚሳተፉ ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.