Fana: At a Speed of Life!

በአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ፒ ኤስ ጂ እና ሊቨርፑል ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 10 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ትናንት ምሽት ተጀምረዋል፡፡

በምሽቱ ሁለት ጨዋታዎች ሲደረጉ ፒ ኤስ ጂ እና ሊቨርፑል ድል ቀንቷቸዋል፡፡

በካምፕ ኑ ባርሴሎና ከፒ ኤስ ጂ ባደረጉት ጨዋታ የፈረንሳዩ ክለብ በሰፊ የጎል ልዩነት ባርሴሎናን አሸንፏል፡፡

በጨዋታው ባርሴሎናዎች ባገኙት የፍጹም ቅጣት ምት ጨዋታውን መምራት ቢችሉም በኪሊያን ምባፔ ሶስት እንዲሁም በሞይስ ኪን 1 ጎል ፒ ኤስ ጂ ጨዋታውን 4 ለ 1 አሸንፏል፡፡

ኪሊያን ምባፔም በጨዋታው ሐት ትሪክ ሰርቷል፡፡

በሌላኛው ጨዋታ ደግሞ ከሜዳው ውጭ ከጀርመኑ አር ፒ ሌፕዚግ ጋር የተጫወተው ሊቨርፑል 2 ለ 0 ማሸነፍ ችሏል፡፡

በጨዋታው ሞሃመድ ሳላህ እና ሳዲዮ ማኔ ለሊቨርፑል የድል ጎሎቹን አስቆጥረዋል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፦ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ዩቲዩብ ቻናል፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.