Fana: At a Speed of Life!

በአዲስ አበባ ትናንት የጣለው ዝናብ ባስከተለው የጎርፍ አደጋ አንድ ተማሪ መውሰዱ ተነገረ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ትናንት በጣለው ዝናብ አንድ ተማሪ በጎርፍ እንደተወሰደ ተነገረ።

ተማሪው በጉለሌ ክፍለ ከተማ በሚገኘው ላዛሪስት የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ትምህርት ቤት ተማሪ መሆኑም ነው የተመለከተው፡፡

ተማሪው በጎርፍ የተወሰደው በትናንትናው ዕለት ዘጠኝ ሠዓት አካባቢ በጣለው ዝናብ መሆኑን የአዲስ አባባ እሳትና ድንገተኛ አደጋ የኮሙኒኬሽን ባለሙያ የሆኑት አቶ ንጋቱ ማሞ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል፡፡

በጎርፉ የተወሰደው ተማሪ በትምህርት መውጫ ሠዓት ላይ ከትንሽ ወንድሙ ጋር ወደ ቤት እየሄዱ እንደነበርም ተገልጿል፡፡

እስከዛሬ ጠዋት የእሳትና ድንገተኛ አደጋ ሠራተኞቹ ከኅብረተስቡ ጋር በመሆን ተማሪውን የመፈለጉን ሥራ ቀጥለዋል ተብሏል፡፡

ወላጆች በክረምቱ ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ሲልኩም ሆነ ሲቀበሉ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉላቸው የእሳትና ድንገተኛ አደጋ በመልዕክቱ አሳስቧል፡፡

በሲሳይ ጌትነት

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.