Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያ የመስቀል በዓል በተለያዩ ኩነቶች እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ)የመስቀል በዓል በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ከተማ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስነ ስርዓቶች እየተከበረ ነው።

በበዓሉ አከባበር ስነ ስርዓት ላይ የሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ህሩያን እስጢፋኖስ ጥፍጤን ጨምሮ በርካታ ምዕመናን ተገኝተዋል።

ሥራ አስኪያጁ ለምዕመናን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን÷ ምዕመናን በዓሉን በሽብር ቡድኑ ህወሓት ወረራ የተፈናቀሉ ዜጎችን በማሰብ እና በመርዳት እንዲያከብሩም አሳስበዋል።

የሽብር ቡድኑ በሰሜን ጎንደር ዞን ሰባት የሚደርሱ አብያተ ክርስቲያናትን ማውደሙን ም አንስተዋል።

በመላኩ ገድፍ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.