Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያ ከኮሮናቫይረስ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 3 ደረሰ

አዲስ አበባ፣መጋቢት 24፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኮሮናቫይረስ ከተያዙት ሰዎች መካከል አንድ ተጨማሪ ሰው ማገገሙን የጤና ሚኒስቴር ገለጸ።

ከዚህ ቀደም ከህመሙ ማገገማቸው ከተገለጸው ሁለት ህሙማን በተጨማሪ ሌላ ሶስተኛ ሰው ማገገሙን ዶክተር ሊያ ታደሰ ተናግረዋል።

ከዚም ባለፈ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 65 የላቦራቶሪ ናሙና ምርመራ ተካሂዶ ሁሉም ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸው ተገልጿል።

በለይቶ ማቆያ ማዕከል ውስጥ 25 የኮሮናቫይረስ ታማሚዎች መኖራቸውን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ገልጸዋል።

ሚኒስትሯ  አንድ ታማሚ በጽኑ ህሙማን ክፍል ውስጥ እንደሚገኝ  መጠቆማቸውን  ኢ.ዜ.አ ዘግቧል፡፡

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.