Fana: At a Speed of Life!

በውሃ ላይ የሚሰራ የኤሌክትሪክ ብስክሌት በገበያ ላይ ዋለ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 29፣ 2012 (ኤፍቢሲ) በውሃ ላይ የሚሰራ የኤሌክትሪክ ብስክሌት በገበያ ላይ መዋሉ ተነገረ።

ማንታ 5 የተባለው የኒውዝላንድ ኩባንያ ኤክስ ኢ 1 የተሰኘችውን እና በውሃ ላይ የምትሰራውን የኤሌክትሪክ ብስክሌት በላስ ቬጋስ አስተዋውቋል።

ብስክሌቱ በፔዳል የሚሰራ ሲሆን፥ አንድ ጊዜ ባትሪ ከተሞላ በኋላ ለአንድ ሰዓት ያክል መጠቀም ይቻላል።

በሰዓትም እስከ 20 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር ድረስ መጓዝ ይችላልም ነው የተባለው።

አዲሱ ብስክሌት የ6 ሺህ ፓውንድ ዋጋ ተቆርጦለታል።

ብስክሌቱን ለዕይታ ለማብቃት እስከ 10 አመት ጊዜ እንደፈጀ ኩባንያው ምርቱን ባስተዋወቀበት ወቅት ገልጿል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.