በጌዴኦ ዞን ቡሌ የምርጫ ክልል ከ12 ሰዓት ጀምሮ እየተካሄደ ነው
አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ)በጌዴኦ ዞን ቡሌ የምርጫ ክልል የሚደረገው ዳግም ምርጫ ከ12 ሰዓት ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል።
በምርጫ ክልሉ በአጠቃላይ 83 የምርጫ ጣቢያዎች ያሉ ሲሆን÷ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች አስፈላጊ ቁሳቁስ መሰራጨቱን የጌዲኦ ዞን ምርጫ ቦርድ አስተባባሪ አቶ ሲሳይ አበባየሁ ገልጸዋል።
ከጸጥታ ጋር በተያያዘ ሰላማዊ መሆኑን አንስተው በሁሉም ጣቢያዎች የጸጥታ አካላት መመደባቸውን አስታውቀዋል።
በምርጫ ክልሉ 3 የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚሳተፉ መሆናቸውን ገልፀው÷ ብልጽግና፣ ጌህዴድ እና ኢዜማ መሆናቸውን መናገራቸውን ደሬቴድ ዘግቧል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!