Fana: At a Speed of Life!

በጎንደር ከተማ የሚገነባው የወጣቶች ማዕከል የመጀመሪያ ዙር ግንባታ 98.8 በመቶ ደረሰ

 

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 4፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር ከተማ አሮጌው ማረሚያ ቤት ሚገነባው የወጣቶች መዝናኛ ማዕከል የመጀመሪያ ዙር ግንባታ 98 ነጥብ 8 በመቶ ደረሰ፡፡

በመጀመሪያ ዙር ግንባታው የሜዳ ቴንስ ፣ቮሊቮል ፣11 ሱቆች ፣ለአዛውንቶች የገበጣና የቸዝ አና የህፃናት መጫወቻ የያዘ ነው ፡፡

የይላቅ ፍቃዱ ህንጻ ስራ ተቋራጭ ባለቤት እና ስራ አስኪያጅ አቶ ይላቅ ፍቃዱ እንደተናገሩት በ15 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር በአንድ ዓመት ለመገንባት ውል ተገብቶ በ3 ወር ከ 26 ቀን ፕሮጀክቱን 98 ነጥብ 8 በመቶ ማድረስ መቻሉን ከከተማ አስተዳደሩ ኮሚዩኒኬሽን መረጃ ያመለክታል፡፡

ፕሮጀክቱ ለየት የሚያደርገው በቀን 18 ሰዓታት በመስራት በጎንደር ከተማ እና በአካባቢዋ ጠንካራ የሥራ ባህል እና ትምህርት የሰጠ መሆኑን አቶ ይላቅ ፍቃዱ ተናግረዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.