Fana: At a Speed of Life!

በፕሪሚየር ሊጉ መቐለ 70 እንደርታ ሀዋሳ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 14ኛ ሳምንት ብቸኛ ጨዋታ ዛሬ ተካሂዷል።

ሀዋሳ ከተማን በትግራይ ስታዲየም ያስተናገደው መቐለ 70 እንደርታ 5 ለ1 በሆነ ሰፊ ልዩነት አሸንፏል።

የመቐለ 70 እንደርታን የማሸነፊያ ግቦች ኦኪኪ አፎላቢ፣ ሙሉጌታ ወልደጊዮርጊስ እና ቢያድግልኝ ኤልያስ አስቆጥረዋል።

የሀዋሳ ከተማን ብቸኛ የማስተዛዘኛ ግብ ደግሞ ብሩክ በየነ አስቆጥሯል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.