Fana: At a Speed of Life!

በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ቡና እና ወልቂጤ ከተማ አቻ ተለያዩ  

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 13ኛ ሳምንት የመጨረሻ መርሃ ግብር ጨዋታ ዛሬ ተካሂዷል።

በዚህም ኢትዮጵያ ቡና እና ወልቂጤ ከተማ በአዲስ አበባ ስታዲየም ባደረጉት ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።

የኢትዮጵያ ቡናን ብቸኛ ግብ ፍቅረየሱስ ተክለብርሀን በ29ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።

የወልቂጤ ከተማን ግብ ደግሞ አህመድ ሁሴን ጨዋታው በተጀመረ 10ኛው ደቂቃ ላይ ኳስን ከመረብ አገናኝቷል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.