Fana: At a Speed of Life!

በ500 ሺህ ብር የተገነባው የቡና ኮንትራት አስተዳደር ሶፍትዌር ስራ ጀመረ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 16 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለስልጣን 500 ሺህ ብር ወጪ ያደረገበት የቡና የኮንትራት አስተዳደር ሶፍትዌር ስራውን ጀመረ፡፡

የግብር ሚኒስትሩ አቶ ዑመር ሁሴን የኮንትራት ውል አስተዳደር ወደ ስራ መግባቱ የተንዛዛውን የግብይት ስርዓት ከማስቀረት ባሻገር ረጅም ጊዜ የሚፈጀውን የግብይት ሂደት በ5 ደቂቃ እንዲያልቅ የሚያደርግ ነው ብለዋል፡፡

እንዲሁም ህገ ወጥ ግብይትን እና ኮንትሮባንድን ያስቀራል ተብሏል፡፡

በባለስልጣኑ ግቢ ውስጥ ዘመናዊ የሆነ የቡና ጥራት መመርመሪያ፣ የቅምሻ እና የባሬስታ ማሰልጠኛ ማዕከል ስራ ጀምሯል፡፡

ይህም ኢትዮጵያ ዘንድሮ ለምታዘጋጀው የባለ ልዩ ጣዕም የቡና ውድድር የራሱን አስተዋፅኦ ያበረክታል ነው የተባለው፡፡

የግንባታው ሙሉ ወጪም በተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት (ዩኒዶ) እና በጣሊያን ኮርፖሬሽን ተሸፍኗል፡፡

በሲሳይ ሃይሌ

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል www.youtube.com/fanatelevision ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
593
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.