Fana: At a Speed of Life!

ባለፉት 24 ሰዓታት 959 የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው 735 ሰዎች አገግመዋል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት 24 ሰዓታት በተካሄደ 8 ሺህ 101 የላብራቶሪ ምርመራ 959 የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።
በዚህ በኢትዮጵያ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 78 ሺህ 819 ደርሷል።
ባለፉት 24 ሰዓታት ከቫይረሱ ምክንያት የ8 ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን በኢትዮጵያ በቫይረሱ ምክንያት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 1 ሺህ 222 መድረሱ ተነግሯል።
እንዲሁም በ24 ሰዓታት ውስጥ 737 ከቫይረሱ ያገገሙ ሲሆን በዚህም በአጠቃላይ ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 33 ሺህ 60 ዶክተር ሊያ አስታውቋል።
በአሁን ወቅት 44 ሺህ 535 ሰዎች ቫይረሱ የሚገኘባቸው ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ 285ቱ ፅኑ ህሙማን መሆናቸው ተጠቁሟል።
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.