Fana: At a Speed of Life!

ቱርክ በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ዘርፍ ለመሰማራት ፍላጎት እንዳላት ገለፀች

አዲስ አበባ ፣ ጥር 6 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል የተመራ ልዑክ በቱርክ ኢስታንቡል ከቱርክ ቢዝነስ ካውንስልና በኢትዮጵያ በተለያዩ ኢንቨስትመንት መስኮች ከተሰማሩ ባለሃብቶች ጋር ተወያይቷል፡፡

በውይይቱ የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የጉምሩክ ቀረጥ፣ የባንክ ዋስትና አሰጣጥ፣ የህግ ማስከበር ስራዎችን ጨምሮ ሌሎች የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ያሉ ክፍተቶች በተሳታፊዎች ተነስተው ሚኒስትሩ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

በቱርክ በኩልም በቀጣይ በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት ዘርፍ የበለጠ ለመስራት ያላቸውን ፍላጎት መግለፃቸውን ከንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.