Fana: At a Speed of Life!

አሜሪካ ኢትዮጵያ ላይ ልትጥል ያሰበችውን ማዕቀብ ቻይና ተቃወመች

 

አዲስ አበባ፣ መስከረም 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ልትጥል ያሰበችውን አዲስ ማዕቀብ እንደምትቃወም ቻይና አስታወቀች፡፡

የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሊጂያን ዣዎ ፥አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ለመጣል ያሰበችው ማዕቀብ ቻይና ትቃወማለች ብለዋል በቲውተር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ፡፡

አሜሪካ በጥንቃቄ ገንቢ ሚናዋን ትወጣለች ብለን እናምናለንም ብለዋል ቃል አቀባዩ፡፡

ኢትዮጵያውያን ልዩነቶችን ለመፍታት፣ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር፣ ሠላምና ጸጥታዋን ለማረጋገጥ አቅሙም ጥበቡ እንዳላት እናምናለን ብለዋል ቃል አቀባዩ።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.