Fana: At a Speed of Life!

አምባሳደር ሂሩት የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዚዳንት አቀረቡ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 4 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አምባሳደር ሂሩት ዘመነ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዚዳንት አቀረቡ።

ተቀማጭነታቸው በቤልጂየም፣ ብራስልስ ሆኖ በሉግዘምበርግ እና በአውሮፓ ህብረት ተቋማት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሂሩት ዘመነ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ሌይን አቅርበዋል።

በወቅቱም የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታዎችን በተመለከተ ውይይት ማድረጋቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.