አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ በሱዳን ከአውሮፓ ሕብረት አምባሳደር ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በሱዳን የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ በሱዳን ከአውሮፓ ሕብረት አምባሳደር ሮበርት ቫን ደን ዱል ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ተወያዩ፡፡
ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ ከህብረቱ አምባሳደር ጋር የተወያዩት በትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ፣ በኢትዮጵያ-ሱዳን የድንበር ጉዳይ እና በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ነው፡፡
አምባሳደር ይበልጣል በውይይቱ የኢትዮጵያን አቋም ለህብረቱ አምባሳደር ማስረዳታቸውን በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን