Fana: At a Speed of Life!

አቶ ደመቀ መኮንን ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ወደ ቱርክ ሊያቀኑ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ወደ ቱርክ ሊያቀኑ ነው፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በቱርክ ለሁለት ቀናት የሚያደርጉትን ጉብኝት ነገ ይጀምራሉ ተብሏል፡፡

በቆይታቸውም በሁለቱ ሃገራት የጋራ ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩ ነው የተገለጸው፡፡

እንዲሁም ዓለም አቀፋዊና ቀጠናዊ ጉዳዮችም እንደሚነሱ ተሰምቷል፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በቱርክ ቆይታቸው አንካራ የተገነባውን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ይመርቃሉ ተብሏል፡፡

ሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከጀመሩ 125 ዓመታትን ማስቆጠራቸውን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

 

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤

ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ

ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን

የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት መተግበሪያን https://play.google.com/store/apps/details… በስልክዎ በመጫን ቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት፣ ኤፍኤም 98.1 እና ብሄራዊ ሬዲዮን ይከታተሉ፡፡ ቪዲዮዎችንም ይመልከቱ፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.