አየር መንገዱ ሁለት አዳዲስ ኤርባስ A-350 አውሮፕላኖችን ተረከበ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሁለት አዳዲስ ኤርባስ A-350 አውሮፕላኖችን በዛሬው እለት ተረክቧል።
ሁለቱም ኤርባስ A-350 አውሮፕላኖች በዛሬው እለት አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ደርሰዋል።
ኤርባስ A-350 አውሮፕላኖቹ ወደ አዲስ አበባ ሲመጡም ለኢትዮጵያ ድጋፍ የተደረጉ የተለያዩ የህክምና ቁሳቁሶችን ጭነው መምጣታቸውንም ከአየር መንደጉ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በዛሬው እለት በተካሄደው ስነ ስርዓት ላይም ኤርባስ A-350 አውሮፕላኖቹ ጭነውት የመጡት የህክምና ቁሳቁስ ለጤና ሚኒስቴር ተበርክተዋል።