Fana: At a Speed of Life!

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአፍሪካ ምርጡ 10ኛ ዩኒቨርሲቲ ተባለ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአፍሪካ ምርጡ 10ኛ ዩኒቨርሲቲ ተባለ።

ዩኤስ ኒውስ ግሎባል ዘንድሮ ባወጣው ደረጃ መሰረት ዩኒቨርሲቲው ከአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች 10ኛ ደረጃ ሲይዝ በምስራቅ አፍሪካ ደግሞ ቀዳሚ ሆኗል።

በዓለም ላይ ካሉ ዩኒቨርሲቲዎች አንጻር ደግሞ 553ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

ባለፈው አመት ኒውስ ግሎባል ባወጣው ደረጃ ከምስራቅ አፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች 2ኛ እንዲሁም ከዓለም 616ኛ ደረጃ ላይ የነበረው ዩኒቨርሲቲው ዘንድሮ ደረጃውን አሻሽሏል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.