Fana: At a Speed of Life!

አዲስ የመንገድ ደህንነት እና ኢንሹራንስ ፈንድ አገልግሎት ደንብ በመጠናቀቅ ላይ ነዉ – ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ አዲስ የመንገድ ደህንነት እና ኢንሹራንስ ፈንድ አገልግሎት ደንብ በመጠናቀቅ ላይ መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ ገለጹ፡፡

ወ/ሮ ዳግማዊት በትዊተር ገጻቸዉ ባሰፈሩት ጽሁፍ እንዳስታወቁት አዲስ የመንገድ ደህንነት እና ኢንሹራንስ ፈንድ አገልግሎት ደንብ በመጠናቀቅ ላይ ሲሆን፥ ከመንገድ ፈንድ ክፍያዉ ቢያንስ አምስት በመቶው ለድህረ-ድንገተኛ ህክምና አገልግሎት ወጭዎች የሚመደብ ነዉ ብለዋል።

ይህም ከመንገድ ደህንነት ጋር በተያዘ የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ ተጨማሪ ፋይናንስ ለማግኘት ይረዳል ነው ያሉት፡፡

ለአፍሪካ እና ሌሎች ታዳጊ የአለም አገራት የመንገድ ደህንነት ትልቅ ትኩረት መስጠት አማራጭ ሳይሆን ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን የጠቆሙት ሚንስትሯ፥ በኢትዮጵያ የመንገድ ደህንነት ላይ መስራት ወጪ ሳይሆን ወሳኝ ኢንቨስትመንት ነውም ብለዋል፡፡

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.