Fana: At a Speed of Life!

አፍሪካውያን በአንድነት መቆም አለብን – ፕሬዚዳንት ማኪ ሳል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ)አፍሪካውያን በአንድነት በመቆም በአለም ላይ ያለንን ድርሻና ጥቅም አስጠብቀን መቆየት አለብን ሲሉ የሴኔጋል ፕሬዚዳንት ማኪ ሳል ገለጹ፡፡

ፕሬዚዳንቱ ይህን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከቀናት በፊት በትዊተር ገጻቸው አስፍረውት የነበረውን መልዕክት በመጋራት ነው፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባሰፈሩት መልዕክትም ‘’የእኛ የአፍሪካውያን ትብብር ለሁለንተናዊ እድገት ወሳኝ ነው’’ ብለዋል፡፡

በዚህም ፕሬዚዳንት ማኪ አህጉራችን ብዙ ኢኮኖሚያዊ ዕድሎች አሏት ያሉ ሲሆን÷ በትብብር ይህ እንዲሳካ ማድረግ አለብን ሲሉ በትዊተር መልዕክታቸውን አስፍረዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.