Fana: At a Speed of Life!

አፍሪካውያን ከኢትዮጵያ ጎን መቆማቸው ለፓን አፍሪካኒዝም ዳግም ውልደት በር የሚከፍት ነው – ምሁራን

አዲስ አበባ፣ ህዳር 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አፍሪካውያን ‘ኢትዮጵያ እየተዋጋች ያለችው የአፍሪካን ጦርነት ነው!’ በሚል ከጎኗ መቆማቸው ለፓን አፍሪካኒዝም ዳግም ውልደት በር የሚከፍት እንደሆነ ምሁራን ገለጹ፡፡

ምሁራኑ ÷ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለአፍሪካውያንና ለጥቁር ህዝቦች ያቀረቡት ጥሪ ወቅቱን የጠበቀ የተገባ ነው ብለዋል፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የአፍሪካና እስያ ጥናትና ምርምር ማዕከል ተመራማሪው ዶክተር ሳሙኤል ተፈራ ÷ በተለይም ድህረ ለውጥ የአፍሪካ ችግር በአፍሪካዊያን የሚል ጠንካራ መንግስት መመስረቱ፣ ከህዳሴ ግድብ ድርድር እስከ ምርጫ የተሄደበትን መንገድ፣ ተላላኪ መንግስት የመመስረት የምዕራባውያን ፍላጎት መጨንገፉ ÷ ምዕራባዊያን በአፍሪካ ሰማይ ስር ማየት ከሚፈልጉት መቃረኑ የውክልና ጦርነት እንዲከፍቱ ማድረጉን ያነሳሉ፡፡

የአፍሪካ ጉዳዮች ተመራማሪው ዶክተር ብርሃኑ ሌንጅሶ በበኩላቸው÷ ‘ኢትዮጵያ የአፍሪካን ጦርነት እየተዋጋች ነው’ በሚል የሚነሳው የአፍሪካዊነት አቀንቃኞች ሀሳብ እውነታውን የገለጠ መሆኑን ያክላሉ፡፡

ዶክተር ብርሃኑ ኢትዮጵያ ማሸነፏ የአፍሪካና የጥቁር ህዝቦች ማሸነፍ ሆኖ እንደሚቆጠር ያነሳሉ፡፡

ይህም ምዕራባውያን ከሚሄዱበት የእጅ አዙር መንገድ የሚገታ ለጥቁር ህዝቦች ሁሉ የይቻላል ስነልቦና የሚገነባ ድል የሚያደርገው ነው፡፡

በዚህ መሃል ግን የአሜሪካና አጋሮቿ ጣልቃ የመግባት ፍላጎት ይነሳል፡፡

ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉ ምሁራን እድል በፈተናዎች ውስጥ እንደሚወለድ አንስተው ÷ ይህ ወቅት ለፓን አፍሪካኒዝም መወለድ እንደመልካም አጋጣሚ ይቆጠራል ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ መነካት በቃ ሲሉ ድምፃቸውን ያሰሙትን አፍሪካውያንና ሌሎችን በማስተባበር ኢትዮጵያ ቀዳሚ ሚና መጫወት ይጠበቅባታል እንደዶክተር ብርሃኑ ሌንጂሶ ሀሳብ፡፡

በአፈወርቅ እያዩ

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.