ኢሬቻ በሰላማዊ ሁኔታ እንዲከበር አስተዋፅኦ ያደረጋችሁትን ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናችኋለች – ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 23፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) የፍቅር ፣ የይቅርታ እና የአንድነት በዓል የሆነውን ኢሬቻን በሰላማዊ ሁኔታ እንዲከበር አስተዋፅኦ ያደረጋችሁትን ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናችኋለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ፡፡
የ2014 ዓ.ም ኢሬቻ በዓልን በደማቅ ሁኔታ አክብረናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ ኢሬቻ የምስጋና ፣ የዕርቅ እና የሰላም በዓል መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በዚህም የፍቅር ፣ የይቅርታ እና የአንድነት በዓሉን በሰላማዊ ሁኔታ እንዲከበር አስተዋፅኦ ያደረጋችሁትን ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናችኋለች ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!