Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያና ጣሊያን የ22 ሚሊየን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 6 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያና ጣሊያን ለተቀናጀ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች የሚውል የ22 ሚሊየን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ።

ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴና የጣሊያን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሉዊጂ ዲ ማዮ ተፈራርመዋል።

ብድሩ የቡልቡላ፣ ቡሬ፣ይርጋለምና ባአከር የተቀናጀ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ማጠናከሪያና በፓርኮቹ ዙሪያ ለሚቋቋሙ የገጠር ሽግግር ማዕከላት ግንባታ የሚውል ነው ተብሏል።

የብድር ስምምነቱ ኢትዮጵያና ጣሊያን ያላቸውን የኢኮኖሚ ትብብር የሚያጠናክር መሆኑን ነው የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሺዴ ያስታወቁት።

የጣሊያን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሉዊጂ ዲ ማዮ በበኩላቸው፥ ስምምነቱ ጣሊያን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን አጋርነት ለማጠናከር እንደምትሻ የሚያሳይ ነው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.