Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያን ለነገው ትውልድ ስናስረክብ ምቹ የመኖሪያ አካባቢን በመፍጠር መሆን አለበት- አቶ ኡሞድ ኡጁሉ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 30፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያን ለነገው ትውልድ ስናስረክብ ምቹ የመኖሪያ አካባቢን በመፍጠር ጭምር መሆን አለበት ሲሉ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ ገለጹ።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር  ጽህፈት ቤት÷ አቶ ኡሞድ ኡጁሉ በተገኙበት የአካባቢ ማስዋብ ፕሮጀክት የምረቃ ሥነ-ስርዓት አካሂዷል፡፡

በስነ-ስርዓቱ ላይ አቶ ኡሞድ ኡጁሉ አንደገለጹት÷ አካባቢን ለኑሮና ለስራ ምቹ ማድረግ ሁሉም ዜጋ ባህል ሊያደርገው ይገባል።

ጋምቤላን በማጽዳት ለኑሮ ምቹ እና የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ  ሁሉም መረባረብ እንዳለበት ጠቁመው÷ የክልሉ መገናኛ ብዙሃን ተቋም የጀመረውን አካባቢን የማስዋብ ፕሮጀክት በዛሬው ዕለት ለርዕሰ መስተዳድር  ጽህፈት ቤት ሰርቶ ማስረከቡን ገልጸዋል።

በቀጣይም ሌሎች ሴክተር መስሪያ ቤቶች አካባቢን የማስዋብ ስራ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበው÷ በስራው አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር  ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፒተር ሆው በበኩላቸው÷ አገራችን በአረንጓዴ ልማት ለአፍሪካና ለመላው ዓለም አርአያ በመሆን የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነች ነው ብለዋል።

በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ባንቻየሁ ድንገታን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ተጋበዥ እንግዶች መገኘታቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.