Fana: At a Speed of Life!

ከተፈቀደላቸው በጀት በላይ የተጠቀሙ 24 ተቋማት ተገኙ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 14፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) ከተፈቀደላቸው በጀት በላይ የተጠቀሙ 24 ተቋማት መገኘታቸውን የፌደራል ዋና ኦዲተር አስታወቀ።

የፌደራል ዋና ኦዲተር መስርያ ቤት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱ እያቀረበ ባለው ሪፖርት በ24 መሥሪያ ቤቶች በልዩ ልዩ የሒሳብ መደቦች ሳያስፈቅዱ እና በጀት ሳያዘዋውሩ ከተደለደለው በጀት በላይ ወጪ የሆነ ሒሳብ መገኘቱን አረጋግጧል፡፡

ከመደበኛ በጀት 645 ሚሊየን 198 ሺህ ብር በላይ ሆኖ መገኘቱን ነው ያረጋገጠው።

በልዩ ልዩ የሒሳብ መደቦች ከተፈቀደላቸው በጀት በላይ ከተጠቀሙ መሥሪያ ቤቶች መካከልም ፥ የኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርስቲ፣ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፣ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ፣ ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ፣ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ፣ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እና ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተካተዋል።

ተቋማቱ በየሒሳብ ኮዶቹ ከተፈቀደው በጀት ከ10 በመቶ በላይ ያልተጠቀሙበትን ብቻ በመውሰድ ፤ በድምሩ ብር 21 ቢሊየን 12 ሚሊየን 778 ሺህ በላይ ብር ያልተሠራበት በጀት ተገኝቷል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.