Fana: At a Speed of Life!

ከአሉባልታዎች በላይ ኢትዮጵያ ዛሬም የኢንቨትመንቶች አይን ማረፊያ ናት – ኢ/ር ታከለ ኡማ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከአሉባልታዎች በላይ ኢትዮጵያ ዛሬም የኢንቨትመንቶች አይን ማረፊያ መሆኗን የማዕድን ሚኒስትር ኢንጂነር ታከለ ኡማ ገለጹ፡፡

ከአውስትራሊያ፣ ስዊድን፣ ካናዳ፣ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ እና የጣሊያን የማዕድን ኩባንያዎች ጋር ሰፊና ገንቢ ውይይቶች ማድረጋቸውን ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡

ኩባንያዎቹ ÷ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሏቸውን ኢንቨስትመንቶች ከማሳደግ አልፈው ተጨማሪ የማዕድን ኢንቨስትመንቶች ላይ የመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋልም ነው ያሉት፡፡

አክለውም ‘’በኛ በኩል ተገቢውን ድጋፍ እንደሚያገኙ ከስምምነት ደርሰናል’’ ብለዋል፡፡

ውይይቱ ኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ኢንቨስትመንቶችን የመሳብ አቅም እንዳለው ያረጋገጠ ተጨማሪ ማስረጃ መሆኑን አንስተዋል፡፡

በሁሉም ግንባር ትግላችን ይቀጥላል ፤ በመጨረሻም ኢትዮጵያ ታሸንፋለች ብለዋል ኢንጂነር ታከለ በመልዕክታቸው፡፡

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.