Fana: At a Speed of Life!

ወርቅ በሚወጣበት አካባቢ የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ እንዲከፈት ይደረጋል ተባለ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 16፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የወርቅ ምርትን ግብይት ህጋዊ መስመር እንዲይዝ የማስተካከያ ስራዎች እየተሠሩ መሆኑ ተገለፀ፡፡

የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትሩ ኢንጅኒየር ታከለ ኡማና ሌሎች የስራ ሀላፊዎች በደቡብ፣ በሲዳማ፣ በጋምቤላና በቤንሻንጉል ከልሎች ጉብኝት አድርገዋል፡፡

በዚህም የማዕድን ምርት በተለይም የወርቅ ምርትን ማሳደግ በሚቻልበት ዙሪያ ውይይት የተደረገ ሲሆን÷ ወርቅ በሚወጣባቸው አካባቢዎች የንግድ ባንክ ቅርንጫፎችን ለመቋቋም ስምምነት ላይ ተደርሷል።

በውይይቱ የተገኙት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ህጋዊ ግብይት ለማካሄድ የሚያስችሉ የንግድ ባንክ ቅርንጫፎች እንዲከፈቱ ይደረጋል ብለዋል፡፡

በወርቅ ግብይት ላይ የሚታዩ ህገወጥ እንቅስቃሴዎች ስርአት የሚይዙበትን መንገድ ለማመቻቸት ይሰራልም ነው የተባለው፡፡

በቀጣይም በህገወጥ አዘዋዋሪዎች ላይ ጠንካራ ክትትል የሚደረግ ሲሆን÷ በአጠቃላይ የአዘዋዋሪዎች ፍቃድ ላይ ፍተሻ ይካሄዳል ተብሏል፡፡

የፀጥታ ጉዳዮች አፋጣኝ እርምጃ እንዲወሰድባቸው አቅጣጫ ከተቀመጠላቸው ውስጥ መሆኑን ከማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.