Fana: At a Speed of Life!

ወርቅ በስድስት ወራቱ የወጪ ንግድ አፈፃፀም ከፍተኛ ድርሻ ካላቸው ዘርፎች ቀዳሚው ሆኗል

አዲስ አበባ ፣ ጥር 13 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በስድስት ተከታታይ ወራት የወጪ ንግድ አፈፃፀም ከፍተኛ ድርሻ ካላቸው አምስት ዘርፎች መካከል ወርቅ በአንደኝነት መቀመጡ ተገልጿል።

በዚህም መሰረት

1. ወርቅ 335 ነጥብ 54 ሚሊየን ዶላር

2. ቡና 304 ነጥብ 46 ሚሊየን ዶላር

3. አበባ 213 ነጥብ 37 ሚሊየን ዶላር

4. ጫት 187 ነጥብ 82 ሚሊየን ዶላር

5. የቅባት እህሎች 150 ነጥብ 72 ሚሊየን ዶላር ገቢ ያስገኙ ሲሆን የጥራጥሬ ሰብሎች፣ ጨርቃጨርቅና አልባሳት እንዲሁም ኤሌክትሪክ ከስድስት እስከ ስምንት ያለውን ደረጃ ይዘዋል።

ምግብና መጠጥ፣ የስጋ ወተትና ኢንዱስትሪ ዘርፍ፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ የቁም እንስሳት፣ ቆዳና የቆዳ ውጤቶች እና ኤሌክትሮኒክስ እንደየቅደም ተከተላቸው ያለውን ደረጃ መያዛቸውም ነው የተገለጸው።

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.