Fana: At a Speed of Life!

የመንግስት አካላት ከህዝብ የተጣለባቸዉን አደራ በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባ የህግ ባለሙያዎች ጠቆሙ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) አስፈጻሚ አካላት ከህዝብ የተጣለባቸዉን አደራ በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባ ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ያነጋገራቸዉ የህግ ባለሙያዎች ተናገሩ ፡፡

በሚዛን ቴፒ ዪኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ክፍልና የፖለቲካ ጉዳዮች ተንታኝ አቶ መሃመድ ሰኢድ÷ መንግስት የህግ ተጠያቂነትን በአግባቡ ገቢራዊ ማድረግ እንደሚገባው ጠቁመዋል ፡፡

ከአቶ መሃመድ ሰኢድ ሃሳብ ጋር የሚስማሙት እና የህግ ባለሙያና ጠበቃ የሆኑት አቶ ፋሲል ስለሺ በበኩላቸው ÷ አስፈጻሚ አካላቱን ወደ ሌብነት የሚወስዱ ልል የመንግስት አሰራሮች ማሻሻል አለባቸው ብለዋል፡፡

የህግ ባለሙያዎቹ አክለውም ከዚህ ቀደም ጥርስ የሌለዉ አንበሳ ሆኖ የቆየዉ የህዝብ እንደራሴው አካል ጠንካራ እና እዉነተኛ ስራዎችን ተግባራዊ ማድረግ እንዳለበትም ሃሳባቸዉን አካፍለዋል ፡፡

ተሿሚዎች ለጋራ ሃገር በሚደረገዉ ጥረት ውስጥ ለህሊናቸዉ ተጠያቂ በመሆን ከህዝብና ከመንግስት የተጣለባቸውን አደራ በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባም አስረድተዋል ፡፡

በአወል አበራ

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.